ታህሳስ
፳፱ ቀን ፳፻፩
ዓ.ም
በስመ
አብ ወወልድ
ወመንፈስ ቅዱስ
፩ አምላክ አሜን
ብፁዕ
አቡነ አብርሃም
የልደት በዓልን
ምክንያት
በማድረግ
ያስተላለፉት ቃለ
ምዕዳን እና
ቡራኬ

በአለንበት
አገር በሰሜን
አሜሪካ፤
በሀገራችን
በኢትዮጵያና
በልዩ ልዩ
አኅጉራት
የምትገኙ
አባቶቼና
እናቶቼ
ወንድሞቼና
እኅቶቼ ከሁሉ
አስቀድሞ
ለጥበቃዉና
ለመግቦቱ
ወሰን
የሌለበት
ልዑል
እግዚአብሔር
በረድኤት
ጠብቆ ሰላም
እርቅ
ለተመሠረተበት
ሰውና
መላእክት
በአንድነት
ለዘመሩበት
እንኳን
ለብርሃነ
ልደቱ በሰላም
አደረሳችሁ
በማለት
በሀገረ
ስብከቱ ስም
መልካም
ምኞቴን
አቀርባለሁ።
ተጨማሪ
የኢትዮጵያ
ቤተ ክርስቲያን
በሃይማኖት
ለወለደቻቸዉ
ልጆቿ ብቻ
ሳትወሰን ለኢትዮጵያዉያን
ወገኖቿ ሁሉ
የመጀመሪያዉን
ትምህርት ቤት
በመክፈት ሥነ
ጽሑፍን[፣ ሥነ
ጥበብን፣ ሥነ
ስዕልን፣
አስተዳደርን፣
በብቃትና በትጋት
አስተምራለች።
ከዚህም ጋር
በጋራ የአገር
ድንበር
መጠበቅን፣
በሀዘን በደስታ
ተባብሮና
ተደጋግፎ
መኖርን፣
ለትዉልድ ሁሉ
አበርክታለች። አበዉ
እንደሚሉት ታሪክ
ትልቅ ትምህርት
ቤት ከመሆኑም
በላይ መስተዋት
ነዉና ከመልካም
ታሪኳ
እንደተማርነዉና
እንደተረዳነዉ
እዉነተኛ ልጆቿን
ለይታ የምታዉቅ
በመሆኗ መልካም
ስምን ሰጥታ
ሞግስን እና
ክብርን አጎናጽፋ
ትልቅ ትንሽ፣
ነጭ ጥቁር፣ ሩቅ
ቅርብ፣ ዘመድ
ባዕድ ሳትለይ
እናትነቷን
አዉቀዉ፣ ጥሪዋን
ሰምተዉ፣ ሥራቷን
ተቀብለዉ፣ ሕጓን
አክብረዉ
ለሚመላለሱት ሁሉ
አድልዎ በሌለበት
የእናትነት ፍቅሯ
የማይጠፋ
የዘለዓለም ስምና
ክብር ከድል
አክሊል ጋር
አቀዳጅታለች።