:::ዜናዎች:::

:::ያግኙን :::

ርዕሰ አንቀጽ

ወጣቱ ወዴት ነው መሄድ ያለበት)
የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በሃይማኖት ፍቅር በነደዱ፣ ለተጋድሎ ራሳቸውን በሰጡ የአባቶቻቸውን ታሪክ ለመድገም በቆረጡ ታሪክ ሠሪ ወጣቶች የተሞላ ነው፡፡ እነ አቤልን፣ እነ ይስሐቅን፣ እነ ያዕቆብን፣ ነቢዩ ዳንኤልን እና ሠለስቱ ደቂቅን፣ ባሮክን እና አቤሜሌክን በብሉይ ኪዳን እናገኛቸዋለን፡፡Ý
ተጨማሪ

 

 
  ራእይ
 
የጥያቄዎ መልስ
  ሊቀ ጳጳሱን ይጠይቁ
  ስብከቶች

 
 
 


በዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት የምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ተክለሃይማኖት
ቤተ ክርስቲያን /መንበረ ጵጵስና/ቅዳሴ ቤት በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

ክፍል 2        ክፍል 3
ክፍል 4        ክፍል5

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት የምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን /መንበረ ጵጵስና/ ቅዳሴ ቤት ግንቦት 30 ቀን 2001 ዓ.ም /ጁን 7 2009/ በሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ በብፁዕ አቡነ አብርሃም፤

በመሥራች ኮሚቴው እና አባላቱ ከፍተኛ ጥረት በፈቃደ እግዚአብሔር “የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን” በሆነው በበዓለ ጰራቅሊጦስ ቀን በቨርጂንያ (115 ዋሽንግተን ስትሪት አሌክሳንደሪያ ቨርጂንያ) ተከበረ።

በቅዳሴ ቤቱ አከባበር ላይ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤት መዘምራን፣ ቁጥራቸው የበዛ ምእመናን እና ምእመናት ተገኝተው መንፈሳዊ ደስታቸውን በዕልልታና በጭብጨባ አስተጋብተዋል።

ብፁዕነታቸው በክብረ በዓሉ ለተገኙት ምእመናን በአስተላለፉት ቃለ ምእዳን እና ቡራኬ “በሀገረ ስብከቱ የተመሠረተው የመንበረ ጵጵስናው ቤተ ክርስቲያን፤ ሥርዓትን ጠብቆ የተመሠረተ“ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህም ባሻገር “የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፤ ቀኖናና ትውፊት ሳይከለስና ሳይበረዝ ለነገው ተተኪ ትውልድ ለማስተላለፍ እና ለማስረከብ መንፈሳዊ ግዴታ” ያለብን መሆኑን በአጽንዖት ገልጸው “መለያየትን እና መመከፋፈልን ለማስወገድ ይልቁንም የተለያየን አንድ ሆነን የተጣላን ታርቀን የቤተ ክርስትያናችንን ህልውና ጠብቀን ለትውልዱ ማቆየት አማራጭ የሌለው መፍትሄ ከመሆኑም በላይ በመለያየትና በመከፋፈል አንድነትን ማምጣት የማይቻል” መሆኑን አስረድተዋል።

ብፁዕነታቸው ከዚህ በማያያዝ “በመቀራረብና በመመካከር ለችግሮች መፍትሄ በመፈለግ የእናታችን የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ህልውና እንዲጠበቅ፤ ቤተ ክርስቲያናችን የወላድ መካን በመሆን ሀዘንተኛ እንዳትሆን፤ ውድቀቷን ለሚፈልጉ ተቃዋሚዎቿ እንዳትጋለጥ፤ ጉዳዩን በቸልተኛነት ማየት የለብንም” ብለዋል።

በመጨረሻም  “የታሪክ ተወቃሾች እንዳንሆን ልጆችሽ አለን በማለት የሕጓ ጠባቂዎች፣ የሥርዓቷ ፈጻሚዎች እንድንሆን ቤተ ክርስቲያን የእናትነት ጥሪዋን ታስተላልፋለች” ሲሉ ብፁዕነታቸው ለሁሉም ጥሪያቸውን አቅርበዋል። በሌላ መልኩም ሀገረ ስብከቱ በማኅበራዊና መንፈሳዊ ጉዳዮች ላይ ሕገ ቤተ ክርስቲያንን በመጠበቅ ካህናትን እና ምእመናንን በማስተባበር የሚሠራ እና የሚያሠራ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በዚህ መልክ ከሌሊት የተጀመረው አገልግሎት ታቦተ ሕጉ ዑደት አድርጎ ከገባ በሁዋላ በብፁዕነታቸው ጸሎትና ቡራኬ ተጠናቋል።


የዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት መንበረ  ጵጵስና ግዢ ተከናወነ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት ከአንድ ዓመት በላይ በትጋትሲሠራበት የነበረውን የመንበረ ጵጵስና ግዢ በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በድንግል ማርያም አማላጅነት በአባቶችና በምእመናን ትጋትና ርብርብ ተግባራዊ ሊያደርግ

Hagere Sebeket

መቻሉን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አበሰሩ። በትንሣዔ ማግስት፣ በቅ/ሚካኤል ወርሃዊ በዓል መታሰቢያ ዕለት እና በማዕዶት ቀን ይህ ታላቅ ዜና መሰማቱ በአገልግሎቱ የተሳተፉትን በሙሉ ከልብ አስደስቷል።

በቃለ ዐዋዲ ዐንቀጽ አርባ ሦስት ቁጥር አንድ ላይ እንደ ተገለጠው «የመንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በሀገረ ስብከቱ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ገዳማት፣ አድባራት እና የገጠር አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም በየደረጃው ለተቋቋሙት ሰበካ መንፈሳውያን ጉባኤያትና ለወረዳ ቤተ ክህነት የሥራ አመራርና ከፍተኛ የአስተዳደር ኃላፊነት ያለው” እና  በአንድ የተወሰነ ክልል ቤተ ክህነቱን ወክሎ የሚሠራ ተቋም ሲሆን፣ ሃይማኖቱን እና ቀኖናውን ለመጠበቅ እና ለማስጠበቅ፣ ከሐዋርያት  ጀምሮ የመጣውን ሀብተ ክህነት ለመጠበቅ እና ለማስተላለፍ፣ ስብከተ ወንጌል እንዲስፋፋ፣ ገዳማት እና አድባራት እንዲረዱ፣ አብያተ ክርስቲያናት እንዲተከሉ፣ ምእመናን ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኙ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ መብት እንዲከበር፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሎት ወጥ እና ሥርዓቱን የጠበቀ እንዲሆን፣ የካህናት አስተዳደር እና አገልግሎት በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግ መሠረት እንዲሆን፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሀብት እና ንብረት በሕግ እና በሥርዓት መሠረት እንዲጠበቅ፣ ምእመናን በቤተ ክርስቲያኒቱ ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኙ እና እንዲሰጡ ያደርጋል።

ተጨማሪ

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላምና 
    በጤና አደረሳችሁ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ  ፩ዱ አምላክ አሜን
  
 
 
 
በቀሲስ ነህምያ ጌቱ

ታህሳስ ፳፱ ቀን ፳፻፩ ዓ.ም

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን  

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ያስተላለፉት ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ
በአለንበት አገር በሰሜን አሜሪካ፤ በሀገራችን በኢትዮጵያና በልዩ ልዩ አኅጉራት የምትገኙ አባቶቼና እናቶቼ ወንድሞቼና እኅቶቼ ከሁሉ አስቀድሞ ለጥበቃዉና ለመግቦቱ ወሰን የሌለበት ልዑል እግዚአብሔር በረድኤት ጠብቆ ሰላም እርቅ ለተመሠረተበት ሰውና መላእክት በአንድነት ለዘመሩበት እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ በማለት በሀገረ ስብከቱ ስም መልካም ምኞቴን አቀርባለሁ።  

ተጨማሪ

 
 

  የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ምን ለምን እንዴት 

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነትና የአንድነት ፍሬ በተለያዩ አጋጣሚዎች ታይቷል፡፡ይሁን እንጂ አንድነቱ የተጠናከረ ባለመሆኑ የተከሰቱ ችግሮችም አሉ፡፡ ለአንድነቱ መላላት ምክንያት የሆኑቱን በሁለት ከፍሎ መመልከት መልካም ነው ፡፡እነርሱም ዉጫዊና ዉስጣዊ ችግሮች ናችዉ፡፡

ተጨማሪ

 
መኑ አንተ? አንተ ማነህ?  

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሃይማኖት ለወለደቻቸዉ  ልጆቿ ብቻ ሳትወሰን  ለኢትዮጵያዉያን ወገኖቿ ሁሉ የመጀመሪያዉን ትምህርት ቤት በመክፈት ሥነ ጽሑፍን[፣ ሥነ ጥበብን፣ ሥነ ስዕልን፣ አስተዳደርን፣ በብቃትና  በትጋት አስተምራለች። ከዚህም ጋር በጋራ የአገር ድንበር መጠበቅን፣ በሀዘን በደስታ ተባብሮና ተደጋግፎ መኖርን፣ ለትዉልድ ሁሉ አበርክታለች።  አበዉ እንደሚሉት ታሪክ ትልቅ ትምህርት ቤት ከመሆኑም በላይ መስተዋት ነዉና ከመልካም ታሪኳ እንደተማርነዉና እንደተረዳነዉ እዉነተኛ ልጆቿን ለይታ የምታዉቅ በመሆኗ መልካም ስምን ሰጥታ ሞግስን እና ክብርን አጎናጽፋ ትልቅ ትንሽ፣ ነጭ ጥቁር፣ ሩቅ ቅርብ፣ ዘመድ ባዕድ ሳትለይ እናትነቷን አዉቀዉ፣ ጥሪዋን ሰምተዉ፣ ሥራቷን ተቀብለዉ፣ ሕጓን አክብረዉ ለሚመላለሱት ሁሉ አድልዎ በሌለበት የእናትነት ፍቅሯ የማይጠፋ የዘለዓለም ስምና ክብር ከድል አክሊል ጋር አቀዳጅታለች። 

 if you can't read this website click here and install the font. 

ገረ ስብከታችን
ብፁዕ አቡነ አብርሃም ያስተላለፉት ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የአዲ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ያስተላለፉት ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተላለፈ ቃለ ውግዘት 

English Version Letter , Resolution

 
  Biblical
  Patristic
  Others
  Listen Lesson of the week
  Listen Mesbak of the week
  Downlad Songs and Publications
  Discover Ethiopian Orthodox Church History
  Preaching of the week
 
  www.eotc-patriarch.org
  www.eotc-mkidusan.org
 
www.mahiberekidusan.org
  www.tewahedomedia.org
 
www.tewahedo.org
 
www.kidistselassie.org 
Home| Feedback| Webmaster
EOTC-DC Diocese., All Rights Reserved